ከመድረክ ባሻገር፡ ሰርከስ እንደ አስቻይ የጥበብ ዘርፍ| ተክሉ አሻግር ከተሾመ ወንድሙ ጋር| ኮኔክት ፎር ካልቸር አፍሪካ ኢትዮጵያ ፖድካስት

ሰላም ኢትዮጵያ ከኮኔክት ፎር ካልቸር አፍሪካ እንቅስቃሴ ጋር በጋራ ወደ ሚያቀርበው ኮኔክት ፎር ካልቸር አፍሪካ ኢትዮጵያ ፖድካስት እንኳን በደህና መጣችሁ፡፡

በዚህ ክፍል ተሾመ ወንድሙ ከኢትዮጵያ ሰርከስ ብሔራዊ ማኅበር ፕሬዝደንት ከተክሉ አሻግር ጋር በመሆን ሰርከስ ያለምንም ተቋማዊ ድጋፍ ወይም መሰረተ-ልማት እንዴት ህይወትን እንደለወጠ፣ወጣቶችን እንዳበቃ እንዲሁም ኢትዮጵያ በኪነ-ጥበቡ ዘርፍ ያላትን ዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍ እያደረገ እንደሚገኝ አይን ገላጭ ውይይት ያካሂዳሉ፡፡

የሚዳሰሱ ርዕሶች

·         ኢትዮጵያ በሰርከስ ጥበብ ከዓለም አቀፍ መሪዎች መካከል የመሆኗ ሁኔታ

·         ከስር ጀምሮ እስከ ብቁ ባለሞያነት ድረስ ያለ ጉዞ

·         ሰርከስ እንደ ለውጥ እና ዲፕሎማሲ መሳሪያ

·         የሰርከስ ኢኮኖሚያዊ አንድምታ

ይህ ውይይት ለፖሊሲ አውጪዎች፣ የፈጠራ ስራ ላይ ለተሰማሩ ሰዎች እንዲሁም ለህዝብ፤ የፈጠራ ኢንዱስትሪዎች ሀገራትን በመለወጥ ረገድ ያላቸውን ኃይል እንዲገነዘቡ ጥሪ የሚያቀርብ ነው፡፡

ይመልከቱ እንዲሁም ኃሳብዎን ከስር ያጋሩ!

ስለኮኔክት ፎር ካልቸር አፍሪካ እና 1% የብሔራዊ በጀትን ለባህል ስለማዋል እንቅስቃሴ ለመረዳት የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ፡

https://cfcafrica.org/

ይህን ክፍል በስፖቲፋይ (Spotify) እና አፕል ፖድካስት (Apple podcast) ማድመጥ ይችላሉ፡፡

Podden och tillhörande omslagsbild på den här sidan tillhör Connect for Culture Africa. Innehållet i podden är skapat av Connect for Culture Africa och inte av, eller tillsammans med, Poddtoppen.